አብያተክርስቲያናትን በወንጌል ባልተደረሱ ሥ ፍራዎች ማ ባዛት
የኢየሱስ ክርስቶስን ስም እስካሁን ባልሰሙ ት አካባቢዎች የወንጌልን ሥራ እንዴት ትጀምራላችሁ ወይም እንዴት የበለጠ ታስፋፋላችሁ? አብያተ ክርስቲያኖቻችሁ በአካባቢያቸው የሚ ገኙትን ሰዎች በወንጌል ለመድረስ ራዕይ ያላቸው ሆነው ነገር ግን የወንጌል ሠራተኞችን ለመላክና ለመደገፍ መንገድ አጥታችሁ ይሆን? ምናልባትም በቤተክርስቲያናችሁ የሚገኙ ወጣቶች ወንጌልን ለሌሎች ለማካፈል ትልቅ ሸክም እያላቸው ነገር ግን የሥልጠና ዕጥረት ገጥሟቸው ይሆን? ወይም ቤተክርስቲያኖቻችሁ በከፍተኛ ፍጥነት እያደጉ ሆነው ለእነዚህ ቤተክርስቲያኖች የሚያስፈልጓችሁን መሪዎች እንዴት ማሳደግ እንዳለባችሁ ታስቡ ይሆንን? ልትሄዱና ለክርስቶስ ደቀ መዛሙርትን በማብዛት ትዕዛዙን ለመፈፀም እየፈለጋችሁ ነገር ግን ያላችሁ ሃብት (የሰው፣ የገንዘብ፣ የቁሳቁስ) ውስን አድርጋችሁ ይሆናል፡፡ እነዚህ ሁሉ ውስንነቶች በአጥቢያ ቤተ ክርስቲያኖቻችሁ የተለመዱ ገጠመኞች ሆነው ይሆን?
እንግዲያውስ እኛ ልንረዳችሁ ከጎናችሁ ነን! እኛ “ግሎባል ዲሳይፕልስ አሊያንስ” (አለም ዓቀፍ ደቀመዛሙርት ጥምረት) እንባላለን ተልዕኮአችንም አብያተ ክርስቲያናትንና የአማኞች ህብረቶች የድርሻቸውን በማከናወን የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስ ታላቅ ተልዕኮ እንዲወጡ መደገፍ ነው (ማቴ 28፡19-20)፡፡
ለአጥቢያቤተክርስቲያኖቻችሁንህብረት፣ክርስቶስንያማከለ፣ደቀመዛሙርትማፍራትንመሰረትያደረገናተልዕኮ-ተኮርበሆነመልክአርዓያየሚሆንሥልጠናበመስጠትልንረዳችሁእንችላለን፡፡ይህምሥልጠናደቀመዛሙርትሌሎችደቀመዛሙርትንእንዲያፈሩለማድረግ፣ቤተክርስቲያንተካዮችምራሳቸውንበራሳቸውእንዲደግፉናመሪዎችምየኢየሱስክርስቶስንምሳሌነትእንዲከተሉየሚያደርግነው፡፡እያንዳንዱየሥልጠናመርሃ-ግብርበአጥቢያቤተክርስቲያኖቻችሁባለቤትነትሥርየሚሆኑናበአጥቢያዎቹእየተባዙቀጣይነትያላቸውሊሆኑየሚችሉናቸው፡፡
- የደቀመዝሙርነት-ተልዕኮ (ግሎባል ዲሳይፕልስ) ሥልጠና፡ ይህ ሥልጠና ትኩረት የሚያደርገው አማኞችን እውነተኛ የክርስቶስ ደቀመዛሙርት እንዲሆኑ በመርዳት ሌሎችን ደቀመዛሙርት እንዲያደርጉና በወንጌል ያልተደረሱ ህዝቦችን በወንጌል በመድረስ አጥቢያ ቤተክርስቲያናትን መትከል ግቡ ያደረገ ነው፡፡
- የአነስተኛ ሥራ ፈጠራ (ግሎባል አክሰስ)ሥልጠና፡ ይህ ሥልጠና የቤተ-ክርስቲያን ተካዮችን በአነስተኛ ሥራ ፈጠራ በማስታጠቅ ራሳቸውን እየደገፉ ወንጌል በሥፋት ባልደረሳቸው ማህበረሰቦች መካከል አብያተ ክርስቲያናትን እንዲተክሉ ማገዝ ነው፡፡
- መሪዎችን የማጎልበት(ግሎባል ሊድ)ሥልጠና፡ እግዚአብሔርን በመፍራት የክርስቶስን ምሳሌነት የሚከተሉ መሪዎች በአዳዲስ ቦታዎች በተተከሉ አጥቢያ ቤተክርስቲያናት ውስጥ ያለውን የአመራር ፍላጎት የሚያማDሉ መሪዎችን የማፍራት ሥልጠና ነው፡፡
ከላይ በተጠቀሱት ሦስቱም የሥልጠና አቅጣጫዎች የሚሳተፉት ደቀ መዛሙርትን የሚያፈሩ፣ ቤተክርስቲያንን የሚተክሉና መሪዎችን የሚያሳድጉ በተመሳሳይ ሁኔታ ሌሎችን እንዴት እንደሚያሰለጥኑ ይማራሉ፡፡ ይህም አዳዲስ ደቀ-መዛሙርትንና አጥቢያ ቤተክርስቲያናትን የበለጠ የሚያፈራና ሥልጠናውም በጎ ተፅዕኖ እያደረገ እንዲሄድ ያደርገዋል፡፡ ይህንንም “ቤተ-ክርስቲያናትን የማባዛት ስልት” ብለን እንጠራዋለን፡፡ በዚህ ስልት የዓለም አቀፏ የክርስቶስ አካል በተለይም የክርስቶስ አየሱስን የምሥራች ወንጌል ገና ባልሰሙትና ምላሽ ባልሰጡት መካከል ታባዛለች፡፡ ይህ ግባችንም እናንተን ከመሳሰሉ አጥቢያ የክርስቶስ አካል ጋር በመተባበር ሊሳካ እንደሚችል እናምናለን፡፡
እንደ ክርስቶስ አካል የተሰጣችሁን ተልዕኮ እንድትፈጽሙ እንዴት ልንረዳችሁ እንደምንችል ይበልጥ ለመረዳት የግሎባል ዲሳይፕልስ አሊያንስን የስልጠና ዑደትን ይመልከቱ፡፡
ኢየሱስ ክርስቶስን ለአጎራባች ህዝቦች የማ ካፈል ራዕይ
%MCEPASTEBIN%