አብያተክርስቲያናትን ለመትከል ደቀ-መዛሙርትን ማብዛት
የግሎባል ዲሳይፕል (የደቀ-መዝሙርነት-ተልዕኮ) ሥልጠና ግብ ሌሎችን የክርስቶስ ደቀ-መዛሙርት የሚያደርጉ አገልጋዮችን በማስታጠቅ መላክና በብዛት ወንጌል ባልደረሳቸው ህዝቦች መሃል አዳዲስ የአማኞችን ህብረት ማባዛት ነው፡፡
ትኩረታችን የደቀ-መዝሙርነት-ተልዕኮ የሥልጠና መርሃ-ግብር ከፍታችሁ ደቀ-መዛሙርትን የሚያፈሩትን በማሰልጠን ሄደው አዳዲስ ደቀ-መዛሙርትን እንዲያባዙና አብያተ ክርስቲያናትን እንዲተክሉ መርዳት ነው፡፡ የግሎባል ዲሳይፕል ሥልጠና መርሃ ግብር ሰልጣኞች በባህሪያቸው ክርስቶስን እንዲመስሉና የኢየሱስ አምባሳደር በመሆን ሌሎችን የክርስቶስ ደቀ-መዝሙር በማድረግ ዓለምን በወንጌል እንዲደርሱ ማሰልጠን ነው፡፡ ይህ ሥልጠና ሰልጣኞች እግዚአብሔር ለዓለም ያለውን ዓላማ እንዲገነዘቡ በማድረግ በክርስቶስ ተልዕኮ ውስጥ አጋር ሰራተኞች እንዲሆኑ ማድረግ ነው፡፡ የዚህ ሥልጠና መርሃ ግብር-ዓላማ መንፈሳዊ ግንኙነትን ማጎልበት፣ የፀሎት ህይወትን ማሳደግ፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ምስክርነትንና አገልግሎትን ሁሉ ያካተተ ነው፡፡
የግሎባል ዲሳይፕል የሥልጠና መርሃ-ግብር ሰልጣኞች ከ2 ሳምንት እስከ 4 ወራት ለሚደርስ ጊዜ በሙሉ ጊዜ ሥልጠና መስጠት ነው፡፡ ይህንን ሥልጠና ተከትሎ ሰልጣኞች ቢያንስ ከ 4 ሳምንታት እስከ 11 ወራት የሚቆይ የሙሉ ጊዜ የመስክ የወንጌል ስርጭት ያካሄዳሉ፡፡ የመስክ የወንጌል ሥርጭቱን ተከትሎ ከ2 እስከ 3 ቀን የሚቆይ የመስክ አገልግሎት ምዘና ጊዜ እንዲኖራቸውም ይጠበቃል፡፡
የግሎባል ዲሳይፕል ስልጠና መርሃ-ግብር እስከ አንድ ዓመት ለሚደርስ ጊዜ ሊካሄድ ይችላል፡፡
ማንኛውም የግሎባል ዲሳይፕልስ አሊያንስ አካል መሆን የሚፈልግ የደቀ-መዝሙርነት-ተልዕኮ የሥልጠና ፕሮግራም ቢያንስ በሦስት አጥቢያ ቤተ-ክርስቲያናት (ማህበረ-ምዕመናን) ጥምረት ሥር ሆኖ የሚመራ ሊሆን ይገባዋል፡፡
ስለዚህ ጥምር ቤተ-ክርስቲያናቱ መርሃ-ግብሩ በአካባቢው ቀጣይነቱ አስተማማኝ እንዲሆንና እየተባዛ እንዲሄድ የሚያስችል የአመራር ቡድን ያደራጃሉ፡፡ መርሃ-ግብሩን የሚያንቀሳቅሱት ጥምር ቤተ-ክርስቲያናትን የበጀት አቅርቦት መሰረት ያደረገ መጠነኛ የዘር ገንዘብ ድጋፍም ከግሎባል ዲሳይፕልስ አሊያንስ ይደረግላቸዋል፡፡ ይህን ጉዳይ በተመለከተ የበለጠ ለመረዳት የአሊያንሱን አስተባባሪዎች (ፋስልተተሮች) ማነጋገርና የግሎባል ዲሳይፕልን (ደቀ-መዛሙርት-ተልዕኮ) መጽሔት መጠየቅ ትችላላችሁ፡፡
በግሎባል ዲሳይፕል ሥልጠና መርሃ-ግብር አብረን በመሥራት፣ በመማማር' አብረን በመፀለይ፣ ዕውቀትንና፣ ያለንን ሃብት በጋራ በመጠቀም ባጠቃላይ የመርሃ-ግብራችሁን ውጤታማነት መጨመር እንችላለን፡፡
እንዲሁም የእናንተን አዲስ የደቀ-መዝሙርነት-ተልዕኮ መርሃ-ግብር ከሌሎች በዓለም ዙሪያ እየሰሩ ካሉ የግሎባል ዲሳይፕል ሥልጠና መርሃ-ግብሮች ጋር በማገናኘት የምትደጋገፉበትንና የምትበረታቱበትን መንገድ
የደቀመ ዝሙ ርነትናሚ ሲዮናዊ ተልዕኮ